የማህበሩ ድርጂታዊ መዋቅር

የኛ ድንበር ተሻጋሪ ደረጃ 2-ለ የደ/ጭ/ማመ/ባ/ማህበር ድርጂታዊ መዋቅር፣

ማኀበሩ ለመደራጀት በፈለገበት የደረጃ መስፈርት የተዘረዘሩትን መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆኖ ማንኛውም የጭነት ትራንስፖርት ማኀበር የሚከተለው ድርጅታዊ መዋቅር ይኖረዋል፡፡

  1. ጠቅላላ ጉባዔ፣
  2. የውስጥ ኦዲትና ኢንስፔክሽን፣
  3. የሥራ አመራር ቦርድ፣
  4. ሥራ አስኪያጅ፣

በሥራ አስኪያጅ ሥር፡-

  1. አስተዳደር፣
  2. የንብረትና ፋይናንስ፣
  3. የመረጃ፣ ትራፊክ ደህንነት (Safety Unit) እና የኤች. አይ. ቪ. ኤድስ መከታተያ፣
  4. የዕቅድ እና የገበያ ጥናት፣
  5. የኦፕሬሽንና ሥምሪት፣
  6. የስራ ክትትልና ቁጥጥር፣
  7. የቅርንጫፍ ቢሮዎች አስተዳደር፣
  8. የቅርንጫፍ ቢሮዎች ሂሳብ ክፍል እና ገንዘብ ሰብሳቢ፣
  9. የቅርንጫፍ ቢሮዎች የሥምሪት መረጃ ሙያተኛ፣

ከላይ የተዘረዘሩትን የሥራ አካላት የያዘ ድርጅታዊ አወቃቀርን ይከተላል፡፡ ድርጅታዊ አወቃቀር በተቻለ ሁኔታ የሥራ ሂደትን መሰረት ያደረገ /Process Oriented/ የሆነ እንዲሆን ያደርጋል፡፡ በደረጃ መስፈርቱና በሞዴሉ ላይ በተዘረዘረው የሰው ሀይል ልክ አመቺ የስራ ቢሮ ይኖረዋል የቢሮ መገልገያ መሣሪያዎችና ህትመቶች ተዘጋጅተው ስራ ላይ መዋል አለባቸው፡፡