ከአባልነት ስለማቋረጥ

ከአባልነት ስለማቋረጥ፣

የማኀበር አባልነት በሚከተሉት ሁኔታ ሊቋረጥ ይችላል፡-

  1. አባሉ ከማህበሩ በፈቃዱ ለመልቀቅ ጥያቄ ሲያቀርብና ማኀበሩ የሚፈለግበትን ሰነድ የወሰደውን ንብረት በሠነድ ሲያስረክብ፣
  2. በማኀበሩ አባልነት ያስመዘገበው ተሸከርካሪ ከሚሰጠው አገልግሎት ማኀበሩን ሳያሳውቅ ከአቅም በላይ ባልሆነ ምክንያት ከ30 ቀናት በላይ ከስምሪት ያልተሳተፈ ወይም በብልሽት ምክንያት ለተከታታይ ሶስት ወራት ከሥምሪት ውጭ ከነበረ እና ለማኀበሩ ካላመለከተ ፣
  3. የማኀበሩን አባላት የጋራ ጥቅምና ጤናማ የሥራ ሁኔታ በማወክ ፣ለማኀበሩ ደንብና የአሰራር መመሪያዎች መከበር ሕገ-ወጥ እና እንቅፋት የሆነ ሥራ ላይ በመሣተፍ ጥፋት ከፈጸመ የሥራ አመራር፣
  4. ቦርዱ አባሉን ከጥፋቱ ለማረም ጥረት በማድረግ ሊታረም አለመቻሉን  ሲያረጋግጥ በውስጠ ደንብ መሠረት ከማህበሩ አባልነት ሊታገድ ይችላል፡፡