የአባል መብትነና ግዴታ

የአባል መብትነና ግዴታ፣

በጭነት ትራንስፖርት ማኀበሩ አባል የሆነ የተሸከርካሪ ባለንብረት የሚከተሉት መብቶች ይኖሩታል፡-

  1. ማኀበሩ በሚያደርጋቸው ስብሰባዎች በመገኘት የመምረጥም ሆነ የመመረጥ እኩል መብት ይኖረዋል.
  2. ማህበሩ በሚሰጠው ማንኛውም አገልግሎት እኩል የመጠቀም መብት ይኖረዋል፣
  3. በማኀበሩ ያለውን የአባልነት መብት ከራሱ ውጪ ለሌላ ሰው የማይተላለፍ የግል መብት ሲሆን ፣መብቱንም የሚጠበቅለት ይሆናል፣
  4. አንድ የማኀበር አባል በአንድ ተሸከርካሪ ከአንድ ማኀበር በተጨማሪ ወደ ሌላ ማኀበር ሁለት ቦታ ሊመዘገብ አይችልም ከነበረበት ማኀበር መሸኛ በመውሰድ ወደሚፈልገው ማኀበር መቀየር ይችላል፡፡
  5. ማኀበሩ የሚተዳደርበትን ደንብ ፣የሚሰራባቸውን መመሪያዎች እና ከትራንስፖርት አካላት በየጊዜው ለጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት መሻሻል ማደግ የሚወጡ ደንብና መመሪያዎች ጠይቆ የማግኘትና የመውሰድ መብት አለው፣
  6. በማናቸውም የማህበሩ መደበኛና አስቸኳይ የጠቅላላ አባላት ስብሰባ ላይ የመሳተፍ ፣ስለማኀበሩ የስራ እንቅስቃሴ ማደግና መጠናከር፣ሊኖር ስለሚገባው ቀጣይ የአሰራር ማሻሻያ እና የሚስተዋሉ የአተገባበር ችግሮችን ለመፍታት የሚረዱ አስተያየቶችንና የውሣኔ ድምፅ የመስጠት፣
  7. የራሱ ተሸከርካሪ የሰራበትን ሂሳብ ከወጪ ቀሪ በወቅቱ የማግኘት መብት አለው፣
  8. በአባልነት ከተመዘገበበት ማኀበር በራሱ ፈቃድ ለመልቀቅ ቢፈልግ  ዕዳ ወይም ዕገዳ ከሌለበት መሸኛ የማግኘት መብት አለው፣

የማኀበር አባል የሚከተሉት ግዴታዎች ይኖሩታል፡-

  1. የማኀበሩ ጠቅላላ ጉባኤ በምርጫ የሥልጣን ውክልና በተሰጠው የስራ አመራር ቦርድ የሚሰጠውን የጋራ ስራ ለመፈፀም እንዲያስችል የሚተላለፉ መመሪያዎችንና ትዕዛዞችን መፈጸም
  2. ስለ ትራንስፖርት በመንግስት ሚወጡ ደንብና መመሪያዎች አክብሮ በስራ ላይ ማዋል፣
  3. አገልግሎት በሚሰጥበት ተሸከርካሪ ላይ የቴክኒክ ችግር ሲገጥመው ለማኀበሩ ጽ/ቤት ወይም በአቅራቢያው ላለው የሥምሪት ጽህፈት ቤት ማሳወቅና በማኀበሩ ጋራዥ የማስጠገን፣
  4. በመደበኛና ከመደበኛ ውጭ በማኀበሩ የሚሰጠውን የሥምሪት ትዕዛዝ መፈጸም፣
  5. ስለሚያከናውነው የጭነት ትራንስፖርትና በጉዞ ወቅት ስላጋጠመው አጠቃላይ ሁኔታዎች አስፈላጊውን መረጃ ለዚሁ ስራ ለተቋቋሙ መረጃ ማዕከላት መስጠት፣
  6. ለሚጭነው ማንኛውም ጭነት ማኀበሩ ባሠራው መሠረት ውል የመቀበልና በውሉ መሠረት የመፈፀም፣
  7. በተሸከርካሪው የሚጓጓዙ ዕቃዎችን በአግባቡ ተረክቦ በተሟላ ጥንቃቄ ወደ አስፈላጊው ቦታ የማድረስ፣ ኃላፊነት ተግባራዊ እንዲሆን ለማኀበሩ ሙሉ ኃላፊነት መስጠት
  8. ስለተሸከርካሪዎች የጉዞ አፈፃጸም የወጡ መስፈርቶችን መጠበቅና የመረጃ ቅፆችን በአግባቡ በመጠቀም ሥራ ላይ እንዲውል ማኀበሩ በኃላፊነት እንዲመራለት ማድረግ፣
  9. ተሸከርካሪው ላይ የማኀበር አርማ፣ እስቲከር መለጠፍ፣ዓርማው የማኀበሩን አድራሻ እንዳይዝ ከማኀበሩ ጋር መስራት፣
  10. የማኀበሩ አባል በተሸከርካሪው ላይ የሚሰሩ አሸከርካሪና ረዳት በሚቀጥርበት ጊዜ ውል መፈፀም አለበት ፡፡ የውሉ ኮፒም ለተደራጀበት ማኀበር ያቀርባል ከማኀደሩ ጋርም እንዲያያዝ ይደረጋል፡፡
  11. አባሉ በተሸከርካሪው ላይ የሚሠሩ ሾፌሮችና ረዳቶች በውል የማይቀጥር ከሆነ ማኀበሩ ኃላፊነት በመውሰድ ይቀጥርለታል፡፡